ሙሉ ስሜ አልዓዛር ሃይማኖት እባላለሁ፡ የተወለድኩት መስከረም 22/2006 ዓ.ም ጦርኃሎች ሆስፒታል አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሲሆን ከቤተሰቦቼ እንደተረዳሁት በእናቴ ማሕፀን እያለሁ የጀመረው ታሪኬ ብዙ ፈተናዎችን አሳልፌ ዛሬ የደረስኩበት የደረስኩት እግዚአብሔር ስለረዳኝ እንደሆነ ተረድቻለሁ፤ ስለሁሉም እግዚአብሔር ይመስገን፡፡


ሙሉ ስሙ አልዓዛር ሃይማኖት ገብሬ ይባላል፤ የተወለደው መስከረም 22/2006 ዓ.ም ጦርኃሎች ሆስፒታል አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሲሆን በእናቱ ማሕፀን እያለ የጀመረው ታሪኩ ብዙ ፈተናዎችን አሳልፎ ዛሬ የደረሰበት የደረሰው እግዚአብሔር ፈቃዱ ስለሆነና ስለረዳው ነው፤ ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን፡፡
አልዓዛር እንደ ሁሉም ሕፃናት በ9 ውር ከ5 ቀን ሳይሆን በ8 ወር ከ20 ቀን ነበር የተወለደው፡፡እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በመሆናችን እንደ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት በተወለደ በ8ኛው ቀን ሥርዓተ ግዝረት(ግርዛት) በሚፈፀምበት ዕለት አልዓዛር በጠና ታሞ እዛው የተወለደበት ጦርኃይሎች ሆስፒታል በድጋሚ ገባ፤ ጽኑ ህሙማን ክፍል ለ6 ቀን አስተኝተውት ሕክምና እየተደረገት ቆይቶ እግዚአብሔር ፈቅዶ አይተርፍም ሲባል ዳነ፡፡
በ4 ዓመቱ ዴይኬር ሀይሌ ጋርመንት አዲስ አበባ ኮንዶሚኒየም ሩት አካዳሚ በ2010 ዓ.ም ገባ ያኔም ቢሆን መቀመጥ እንጂ መቆም አይችልም ነበር ፤ የመረዳት ችሎታውን አይተው ዝም ብሎ በቃል ከሚማሩት ሕጻናት ጋር እንዲውል ክፍል ውስጥ ወንበር ላይ ያስቀምጡት ነበር፤ ማታ እቤት ሲመጣ እንደተማሪዎቹ ዩኒፎርም የለኝም እኮ ይለን ነበር ትዝ ይለኛል፡፡ የሩት አካዳሚ ባለቤቶችና የሩት አካዳሚ ማህበረሰብ በጣም ይወዱት እንደነበር እና ሁሉም ይረዱት ነበር፤ እግዝአብሔር ብድራቸውን ይክፈላቸው በጣም አመሰግናቸዋለን፡፡
EDUCATION
CERTIFICATES
SKILLS
WORK
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.